" ዕለተ ዐርብ፦ እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይቺ ናት "
#ዳዊት_ፀሐይ ( የፀሐፊው መብቱ የተጠበቀ ነው። )
ይች ዕለት! " 《 ሚጠተ እግዚአብሔር የሆነባት ዕለት ናት! 》
፥ " ይቺ ዕለት! "《 እግዚአብሔር አምላክ አሕዛብን አጥፍቶ! + ትሩፋንን አውጥቶ! ሥራውን የሰራባት ዕለት ናት! 》
፥《 ይቺ ዕለት በነብያት ፥ ካህናት ጉባኤ ሚጠት ይሆናል ፥ ይደረጋል! 》የሚል ቃል የተሰማባት ዕለት ናት::
፥ 《 ይቺ ዕለት እስራኤላዊያን " ከግብፅ! " የወጡባት ቀን ናት። 》
"በጉን! " ሰውተው " ከሰጠነኛው መቅሰፍት ፥ ከአስረኛው ሞተ በኩር! ፥ ከአሥራ አንደኛው ስጥመት! " የዳኑባት ዕለት ናት።
《 ይቺ ዕለት " በደብረ ሲና! " ፥ " ህግ! " የተሠራባት ዕለት ናት፡፡ " 》
《 ይቺ ዕለት " ኖኅን! " የጠበቀው!
" አብርሃምን! " የመራው!
" ከይስሐቅ! " ጋር የተሳረ!
" ከያዕቆብ! " ጋር እንግዳ የሆነ!
" ከዮሴፍ! " ጋር የተሸጠ!
" በሙሴ! " አድሮ ሕዝቡን የመራ! + " ሕግን! " የሰራ!
" ለኢያሱ! " እርስትን የሰጠ! + " ሕዝበ እስራኤልን! " ያወረሰ!
" በዳዊት! " አድሮ ትንቢት የተናገረ!
" በነብያት! " አድሮ ሕዝቡን ያስተማረ!
" ከእመቤታች ከቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደ!
《 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስስለ እኛ ብሎ ሥጋውን የቆረሰባት ፥ ደሙን ያፈሰባት ዕለት ናት። 》
《 ይቺ ዕለት በነብይ " እግዚአብሔር አለኝ " አንተ ልጄ ነህ፥ እኔ ዛሬ ወለድሁህ።"
(መዝሙረ ዳዊት 2:7፤) የተባለው የተፈጸመባት ዕለት ናት። 》
" አንተ ልጄ ነህ! " አለ አካል ዘእም አካል ፥ ባሕርይ ዘእም ባሕርይ ወለድኩህ ሲለው ነው። " እኔ ዛሬ ወለድሁህ።" ሲለው ግን ሁለተኛ የሚወልደው ሁኖ አይደለም። ስለ ሥራው " ሥጋውን ቆርሶ ፥ ደሙን አፍሶ ፥ ሲኦል ወርዶ! " ነፍሳትን ማውጣቱን ሲናገር ነው።
አንድ " አርበኛ! " አለ። ዘምቶ አርጅቷል ፥ ፈጅቶ አፋጅቷል። ህዝቡን ሰብስቦ ፥ ልጁን አስጠርቶ " ልጄ! " ይለዋል። " ዘምቼ አረጀው ፥ ፈጅቼ አፋጀው ፥ አንተ ልጄ ነህ ፥ በርስቴ ውጣበት ፥ በጉልቴ ውረድበት! " ይለዋል። ልጁም " ወጣሁ ልጅ ነኝ ፥ ፈላሁ ጠጅ ነኝ! " ብሎ ፥ " እግሩን ለጠጠር ፥ ደረቱን ለጦር! " ሰጦ ይዘምታል። ሲመለስ " አባቴ! " ፥ " በርስቴ ውጣበት ፥ በጉልቴ ውረድበት! " ብለህ በሰጠኽኝ ቦታ " ከርስት ላይ ርስት ፥ ከጉልት ላይ ጉልት! " ጨምሬበት መጣሁ! " ይለዋል። አባቱም " ቀድሞ ልጄ ነበርክ ፥ ልጅ መሆንክን አስመሰከርክ ፥ እኔ ዛሬ ወለድኩህ! "
እንደ ሚለው ሁሉ " ጌታም ፥ ጌታችን መድኅኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ! " ከአቤል ጀምሮ እስከ ዕለተ አርብ ያሉትን ነፍሳት " ሥጋውን ቆርሶ ፥ ደሙን አፍሶ ፥ በአካለ ነፍስ ሲኦል ወርዶ! " ፥
" እለ ውስተ ሲኦል ፃዑ፦ በሲኦል ያላችሁ ውጡ! "
" ወእለ ውስተ ጽልመት ተከስቱ፦ በጨለማ ያላችሁ ተገለጡ! "
" ወርእዩ ብርሃን ዐቢየ፦ ኑ ብርሃኑን እዩት! "
ብሎ በጠራቸው ጊዜ ፥ በገነት አድርጎ ባረገ ጊዜ ፥ " እኔ ዛሬ ወለድኩህ! " አለው " አባቱ እግዚአብሔር አብ። "

Comments
Post a Comment