Skip to main content

Posts

" የአማልክት አምላክ ፥ የአጋዕዝት ጌታ ፥ የልዑላን ልዑል! " ነው። እርሱ " የእሳት መጎናጸፊያ የተጎናጸፈ ፥ በነደ እሳት ያጌጠ ፥ የተጌጠ ፥ ዙፋኑ፦ የእሳት ፥ መመላለሻው፦ " በዐይን በማይታይ ፥ በእጅ በማይጨበጥ! " ፦ አየር ፥ ጠፈሩ፦ ሰማይ ፥ መንኮራኩሩ፦ደመና ፥ ጎዳናው፦ የባሕር ማዕበል ነው።

 #ዳዊት_ፀሐይ #እንኳን_አደረሳችሁ " ነቢዬ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳንኤል! "፦ " ዙፋኖችም እስኪዘረጉ ድረስ አየሁ ፥ በዘመናት የሸመገለውም ተቀመጠ። ይለዋል " እግዚአብሔር አብን! " ነው። ይህን ጉዳይ " ቅዱስ ጎርጎርዮስ! ፦ " አምላክነ ዘእንበለ ጥንት ፥ ወመድኃኒነ ዘእንበለ ተፍጻሜት! " ፥ " ጥንት የሌለው አምላክ ፥ ፍጻሜ የሌለው መድኃኒት! " እያለ ይጠቅሰዋል። " እሱ ፥ እራሱ፦ " እግዚአብሔር አብ " <<ያለና የሚኖር>> እኔ ነኝ! " (ኦሪት ዘጸአት 3:14፤) እንዲል " ሕልፈት ፥ ውላጤ! " የማይስማማው ፥  " ጉም ፥ ደመና! " የማይጋርደው ፥ " እሳት ፥ ባሕር! " የማይከለክለው ፥ " በዚህ አለ ፥ በዚህ የለም! " የማይባል ፥ " ለዘመኑ ሕልፈት ፥ ለግዛቱ ወሰን! " የሌለው አምላክ ነው። እና ለዘመኑ " ጥንት! " ተብሎ ስለ ማይነገርለት " ነቢዬ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳንኤል! " ፥ " በዘመናት የሸመገለው! " አለው።  ምንም እንኳ ፍጥረት የፈጠረ እርሱ ቢሆንም እርሱ፦ ብርሃናት ሳይመላለሱ ፥ ነፋሳት ሳይነፍሱ ፥ ማያት ( ወንዞች ) ሳይፈሱ ፥ ቀን እና ሌሊት ፥ ክረምት እና በጋ ሳይፈራረቁ እሱ ነበረ። ይሄን ሲያይ " በዘመናት የሸመገለው! " አለው።  እንደ ገናም ነቢዩ " ልብሱም እንደ በረዶ ነጭ፥ የራሱም ጠጕር እንደ ጥሩ ጥጥ ነበረ፤ ዙፋኑም የእሳት ነበልባል ነበረ፥ መንኰራኵሮቹም የሚነድድ እሳት ነበሩ። "(ትንቢተ ዳንኤል 7:9፤) ይለዋል። ቅዱስ ቄ...
Recent posts

የመስቀሉ ነገር.....Dawit tsehay

  የመስቀሉ ነገር..... #ዳዊት_ፀሐይ ( የፀሐፊው መብቱ የተጠበቀ ነው። ) 《 ዐይን ያላየው ፥     ጀሮ ያልሰማው ፥     በሰው ልቡና ያልታሰበ ፥      " እኛ ልንከብርበት እግዚአብሔር ያከናወነው ፥ ዓለም ሳይፈጠር ያነጸው ፥  ያጸናው《 ነገረ መስቀል! 》ነው::   (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 2: 7-10 )  " የምናገረው ነገር! + የማስተምረው ትምርት! " የሰውነት ልባምነት በማታለል አይደለም::  መንፈስ ቅዱስ ባደረብኝ " ቋንቋ! " በመናገር! + መንፈስ ቅዱስ በገለጠው " ምሥጢር! " በመግለጥ ነው::   《 ድዊ በመፈወስ! +       ለምጻም በማንጻት! +       ጋኔን በማውጣት! +        ሙት በማስነሳት! 》ነው::  " ጠቢባን! " ነን ለሚሉ ሰዎች " ጥበብን! "  እነግራቸዋለሁ:: የምነግራቸው " ጥበብ! "  የዚህ ዓለም ነገስታት! + የዚህ ዓለም ፈላስፎች! የሚያዉቁትን " ጥበብ! "  አይደለም::  የዚህ ዓለም ነገስታት! + የዚህ ዓለም ፈላስፎች! የላወቁትን  《 ከእግዚአብሔር የተገኘውን እውነተኛ ጥበብን ነው::  》  ይህን《 " ጥበብ! " አውቀውትስ ቢሆን ኑሮ! + የክብርን ጌታ! + ባልሰቀሉት ነበር!》  ስለዚህም ነገር " ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ! "   《 አባት ሆይ፥ የሰማይና የምድር ጌታ፥ ይህን " ጥበብ! " ከጥበበኞች!  እና ከአስተዋዮች! + ጠበበኛ! እና አስተዋይ!  " ነን! " ከሚሉት " ከጻሕፍተ ሰፈርሳዊ...

በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። Dawit tsehay

  " በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበርና፥ አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል። " (1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2:25፤) #ዳዊት_ፀሐይ ( የፀሐፊው መብቱ የተጠበቀ ነው። ) " እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበር! " አለ 《 እንደ ታመመ በግ! 》 ማለት ነው:: የተመመን በግ ከመጋው ለይተው! +  ከደረቅ ቦታ አስረው! +  ደረቅ ሣር! + ጥሩ ውኃ ይመግቡታል! + ሲድን ታቅፈው ቀስደው ከመንጋው ይጨምሩታል:: " እንደ ታመመ በግ! "  አለ 《 " ታሞ! "  የነበረ ገነትን ያህል ቦታ! +  እግዚአብሔርን ያህል ጌታ!  አጦ የነበረ " አዳም! " ነው:: " 》" ከመንጋው እንደ መለየት! " 《 አዳምም ከማኅበረ መላእክት ተለይቷል! 》"  ከደረቅ ቦታ አስረው! + ደረቅ ሣር! + ጥሩ ውኃ!  እንዲመግቡት! " 《  ነፍሶሙሰ ለጻድቃን ውስተ እደ እግዚአብሔር ወኢለከፎሙ ላህበ ሥቃይ ወኢምንትኒ! 》 እንዲል《 5500 ዘመን በእደ እግዚአብሔር ሲጠበቅ ኑሯል! 》" ሲድን ወስደው ከመንጋው እንዲጨምሩት! " 《 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ባሕርዩን በሕርይ አድርጎ! + ጽንዓ ነፍስን ሰጥቶ አድኖታል! 》  " ክብር ምሥጋና ለአግዚአብሔር ይሁን። "

" ዕለተ ዐርብ፦ እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይቺ ናት " Dawit tsehay

 " ዕለተ ዐርብ፦ እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይቺ ናት "  #ዳዊት_ፀሐይ ( የፀሐፊው መብቱ የተጠበቀ ነው። ) ይች ዕለት! " 《 ሚጠተ እግዚአብሔር የሆነባት ዕለት ናት! 》 ፥ " ይቺ ዕለት! "《 እግዚአብሔር አምላክ አሕዛብን አጥፍቶ! + ትሩፋንን አውጥቶ!  ሥራውን የሰራባት ዕለት ናት! 》 ፥《 ይቺ ዕለት በነብያት ፥ ካህናት ጉባኤ ሚጠት ይሆናል ፥ ይደረጋል!  》የሚል ቃል የተሰማባት ዕለት ናት::  ፥ 《 ይቺ ዕለት እስራኤላዊያን " ከግብፅ! " የወጡባት ቀን ናት። 》 "በጉን! " ሰውተው " ከሰጠነኛው መቅሰፍት ፥ ከአስረኛው ሞተ በኩር! ፥ ከአሥራ አንደኛው ስጥመት! " የዳኑባት ዕለት ናት።   《 ይቺ ዕለት " በደብረ ሲና! " ፥ " ህግ! " የተሠራባት ዕለት ናት፡፡ " 》 《 ይቺ ዕለት  " ኖኅን! " የጠበቀው!   " አብርሃምን! " የመራው!  " ከይስሐቅ! " ጋር የተሳረ!   " ከያዕቆብ! "  ጋር እንግዳ የሆነ!  " ከዮሴፍ! " ጋር የተሸጠ!  " በሙሴ! " አድሮ ሕዝቡን የመራ! + " ሕግን! " የሰራ!  " ለኢያሱ! " እርስትን የሰጠ! + " ሕዝበ እስራኤልን! " ያወረሰ!  " በዳዊት! " አድሮ ትንቢት የተናገረ!   " በነብያት! " አድሮ ሕዝቡን ያስተማረ!  " ከእመቤታች ከቅድስት ድንግል ማርያም  የተወለደ!  《 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስስለ እኛ ብሎ ሥጋውን የቆረሰባት ፥ ደሙን ያፈሰባት ዕለት ናት። 》 《 ይቺ ዕለት በ...

" እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት:- Dawit tsehay

  " እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት፤ ሐሤትን እናድርግ፥ በእርስዋም ደስ ይበለን።" (መዝሙረ ዳዊት 118:24፤)   " እግዚአብሔር የሠራት ቀን ይህች ናት! " ÷ " ይች ዕለት! " 《 ሚጠተ እግዚአብሔር የሆነባት ዕለት ናት! 》+ " ይቺ ዕለት! " 《 እግዚአብሔር ምላክ አሕዛብን አጥፍቶ! + ትሩፋንን አውጥቶ!  ሥራውን የሰራባት ዕለት ናት! 》 ÷《 ይቺ ዕለት በነብያት! + ካህናት! ጉባኤ ሚጠት ይሆናል! + ይደረጋል! 》 የሚል ቃል የተሰማባት ዕለት ናት::  እቺ ቀን " የመዳን! " ቀን ናት። " መድኃኒት! " የሆነባት ቀን " ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ! " ፥ " የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤ እነሆ፥ የመዳን ቀን ዛሬ ነው።" (2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:2) ሚላት " እቺ ቀን! " ናት።  " ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳይያስ! " ፥ " የሠራዊት አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። በተወደደ ጊዜ ሰምቼሃለሁ፥ በመድኃኒትም ቀን ረድቼሃለሁ፤ እጠብቅህማለሁ፥ ምድርንም ታቀና ዘንድ፥ ውድማ የሆኑትንም ርስቶ ታወርስ ዘንድ፥ "(ትንቢተ ኢሳይያስ 49:8) የሚላት " እቺ ቀን! " ናት።  " መድሃኒትም! " አላት  እስራኤላዊያን " ከግብፅ! " የወጡባት ቀን ናት። "በጉን! " ሰውተው " ከሰጠነኛው መቅሰፍት ፥ ከአስረኛው ሞተ በኩር! " ድነውበታል፡፡  አንድም " የኤርትራን ባህር! " ተሻግረው " ከስጥመት! " የዳኑባት ቀን ናት። አንድም " በደብረ ሲና! " ፥...

የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ እና የቤተ አይሁድ ፥ የጸሐፍት ፈሪሳዊያን ፥ የካህናት አለቆች እና የህዝብ ሽማግሌዎች ጥል ምክንያት ምንድን? ነው።

  የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ እና የቤተ አይሁድ ፥ የጸሐፍት ፈሪሳዊያን ፥ የካህናት አለቆች እና የህዝብ ሽማግሌዎች ጥል ምክንያት ምንድን? ነው። ዳዊት ፀሐይ " እጅ ሊጽፈው ፥ ቃል ሊናገረው ፥ ሕሊና ሊመረምረው ከማይችው " ከገናናው ክብር። የተነሳ በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው የሚል ያ ድምፅ በመጣለት ጊዜ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ " ጌትነቱ ፦ከሙሴ ፥ ከኤልያስ በልጧል ፥ አምልኮቱ በልበ ሐዋርያት ጸንቷል ፥ በልበ ሐዋርያት " ክርስቶን ዕሩቅ ብዕሲ ፥ ወንጌልን ዲቃላ ሕግ! " ያለ ሰይጣን ድል ተነስቷል።  " አንድ ልጅም ከአባቱ ዘንድ እንዳለው ክብር የሆነው ክብሩን አየን። " (የዮሐንስ ወንጌል 1:14፤) እንዲል " አባቱ እግዚአብሔር አብ ጌትነቱን፦ በደብረ ሲና ፦ በአምሳለ እሳት እንዳሳየ ፥ እሱም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፦ ጌትነቱን በደብረ ታቦር ፦ በአምሳለ ብርሃን ! " ገልጧል።  አባቱ እግዚአብሔር አብ ፦ በኤልያስ አድሮ አንድ ሙት ፥ በኤልሳ አድሮ ሁለት ሙት እንዳስነሳ ፥ እሱም ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፦ " የአራት ቀን እሬሳ አልአዛርን ፥ የእለት እሬሳ ወለተ ኢያዒሮስን ፥ ወልደ መበለትን አስነስቷል " " እርሱም የክብሩ መንጸባረቅና የባሕርዩ ምሳሌ ሆኖ፥ ሁሉን በስልጣኑ ቃል እየደገፈ! " እንዲል እርሱ ፦ " ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ " ፥ " እግዚአብሔር አብን " በመልክ የሚመስለው ፥ በባሕርይ የሚተካከለው! " ሁኖ " ብርሃነ ፀሐይ ከዓይን ጋር ተዋሕዶ ክበቡን እንዲያስታውቅ ፥ እሱም ሥጋን ተዋሕዶ   ...

ሩሲያ እና ኦርቶዶክስ ሃይማኖት

 ሩሲያ እና ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ዳዊት ፀሐይ በ10ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከባይዛንቲየም ሚስዮናውያን የተቀየሩት ልዑል ቭላድሚር ቀዳማዊ ክርስትናን የሩስያ ሕጋዊ ሃይማኖት አድርጎ ተቀበለ። ከዚያም ለ1,000 ለሚጠጉ ዓመታት ያህል የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የአገሪቱ ዋነኛ ሃይማኖታዊ ተቋም ሆነ። ከእዛ በ1917 ኮሚኒስቶች ሥልጣን ከያዙ በኋላ የሃይማኖት ተቋማት ተጎዱ። የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አብዛኛውን ንብረቷን ለመውረስ ተገደደች። ብዙ መነኮሳት ከገዳማቸው ተፈናቀሉ።  የቀድሞዋ ሶቪየት ኅብረት ሕገ መንግሥት የሃይማኖት ነፃነትን በስም የተረጋገጠ ቢሆንም ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴዎች በጣም ይገድብ ነበር። እናም ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖተኛ መሆን ከኮሚኒስት ፓርቲ አባልነት ጋር እንደማይጣጣም ይቆጠር ነበር። ስለዚህም ግልጽ የሆነ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት አማኝ መሆን ለግለሰብ እድገት እንቅፋት መሆነ ጀመረ።  በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት መንግሥት ከፋሺዝም ጋር በሚደረገው ውጊያ የክርስቲያኖችን እና የአይሁዶችን ድጋፍ በሚፈልግበት ጊዜ የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታይ የሆነ ማንኛውም ግለሰብ እምነቱን በፈለገው መንገድ መግለጽ ይችላል በማለት ፈቀደ። ከእዛ ጦርነቱ ሲያበቃ እንደገና በኦርቶዶክክ ሃይማኖት ላይ ተመልሶ እገዳ መጣል ጀመረ። እ.ኤ.አ. በ 1980 ዎቹ  በ Mikhail Gorbachev የለውጥ አራማጅ አገዛዝ ፣ " a policy of glasnost " የግላኖስት ፖሊሲ (“ክፍትነት”) ወይም የሃይማኖት ነጻነት ታወጀ። ይህም የሃይማኖት አዋጅ የበለጠ መቻቻልን አመጣ። ከዚያ በኋላ ማለትም ከሶቪየት ኅብረት መፍረስ በውኃላ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ነፃነትን እውን ያደረገ እና  በርካታ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተ...