Skip to main content

በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። Dawit tsehay

 

" በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበርና፥ አሁን ግን ወደ ነፍሳችሁ እረኛና ጠባቂ ተመልሳችኋል። "
(1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2:25፤)

#ዳዊት_ፀሐይ ( የፀሐፊው መብቱ የተጠበቀ ነው። )

" እንደ በጎች ትቅበዘበዙ ነበር! " አለ 《 እንደ ታመመ በግ! 》 ማለት ነው:: የተመመን በግ ከመጋው ለይተው! +  ከደረቅ ቦታ አስረው! +  ደረቅ ሣር! + ጥሩ ውኃ ይመግቡታል! + ሲድን ታቅፈው ቀስደው ከመንጋው ይጨምሩታል:: " እንደ ታመመ በግ! "  አለ 《 " ታሞ! "  የነበረ ገነትን ያህል ቦታ! +  እግዚአብሔርን ያህል ጌታ!  አጦ የነበረ " አዳም! " ነው:: " 》" ከመንጋው እንደ መለየት! " 《 አዳምም ከማኅበረ መላእክት ተለይቷል! 》"  ከደረቅ ቦታ አስረው! + ደረቅ ሣር! + ጥሩ ውኃ!  እንዲመግቡት! " 《  ነፍሶሙሰ ለጻድቃን ውስተ እደ እግዚአብሔር ወኢለከፎሙ ላህበ ሥቃይ ወኢምንትኒ! 》 እንዲል《 5500 ዘመን በእደ እግዚአብሔር ሲጠበቅ ኑሯል! 》" ሲድን ወስደው ከመንጋው እንዲጨምሩት! " 《 ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም ባሕርዩን በሕርይ አድርጎ! + ጽንዓ ነፍስን ሰጥቶ አድኖታል! 》 

" ክብር ምሥጋና ለአግዚአብሔር ይሁን። "


Comments