ሩሲያ እና ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ዳዊት ፀሐይ በ10ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከባይዛንቲየም ሚስዮናውያን የተቀየሩት ልዑል ቭላድሚር ቀዳማዊ ክርስትናን የሩስያ ሕጋዊ ሃይማኖት አድርጎ ተቀበለ። ከዚያም ለ1,000 ለሚጠጉ ዓመታት ያህል የሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የአገሪቱ ዋነኛ ሃይማኖታዊ ተቋም ሆነ። ከእዛ በ1917 ኮሚኒስቶች ሥልጣን ከያዙ በኋላ የሃይማኖት ተቋማት ተጎዱ። የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አብዛኛውን ንብረቷን ለመውረስ ተገደደች። ብዙ መነኮሳት ከገዳማቸው ተፈናቀሉ። የቀድሞዋ ሶቪየት ኅብረት ሕገ መንግሥት የሃይማኖት ነፃነትን በስም የተረጋገጠ ቢሆንም ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴዎች በጣም ይገድብ ነበር። እናም ኦርቶዶክሳዊ ሃይማኖተኛ መሆን ከኮሚኒስት ፓርቲ አባልነት ጋር እንደማይጣጣም ይቆጠር ነበር። ስለዚህም ግልጽ የሆነ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት አማኝ መሆን ለግለሰብ እድገት እንቅፋት መሆነ ጀመረ። በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት መንግሥት ከፋሺዝም ጋር በሚደረገው ውጊያ የክርስቲያኖችን እና የአይሁዶችን ድጋፍ በሚፈልግበት ጊዜ የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታይ የሆነ ማንኛውም ግለሰብ እምነቱን በፈለገው መንገድ መግለጽ ይችላል በማለት ፈቀደ። ከእዛ ጦርነቱ ሲያበቃ እንደገና በኦርቶዶክክ ሃይማኖት ላይ ተመልሶ እገዳ መጣል ጀመረ። እ.ኤ.አ. በ 1980 ዎቹ በ Mikhail Gorbachev የለውጥ አራማጅ አገዛዝ ፣ " a policy of glasnost " የግላኖስት ፖሊሲ (“ክፍትነት”) ወይም የሃይማኖት ነጻነት ታወጀ። ይህም የሃይማኖት አዋጅ የበለጠ መቻቻልን አመጣ። ከዚያ በኋላ ማለትም ከሶቪየት ኅብረት መፍረስ በውኃላ የኦርቶዶክስ ሃይማኖት ነፃነትን እውን ያደረገ እና በርካታ የሕብረተሰብ ክፍሎች የተ...